ከትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ ያሉት ዕለታት ስያሜያቸውና ታሪካዊ አመጣጣቸው

ዲያቆን ተመስገን ዘገየ

ከትንሣኤ ሌሊት ፩ ሰዓት ጀምሮ እስከ ዳግም ትንሣኤ ያለው ሳምንት የፉሲካ ምሥጢር የተገለጠበት፤ ከግብፅ ወደ ምድረርስት ከሲኦል ወደ ገነት መሻገርን የሚያመላክት ሳምንት ነው። ለፉሲካ የሚታረደውም በግ ፉሲካ ይባላል (ዘዳ. ፲፮÷፪:፭÷፮)፤ ፉሲካ ማለት ደግሞ ማለፍ ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትም ሳምንት የፉሲካ ሳምንት ነበር፤ (ሉቃ. ፳፪፥፲፬-፲፮፤ ዮሐ. ፲፰፥፴፰-፵)።

እርሱም ንጹሕ የእግዚአብሔር በግ ሆኖ ደሙን ስላፈሰሰልን ፉሲካችን ክርስቶስ ተባለ፤ ብሉይ ደግሞ የሐዲስ አምሳል ነው። ይኸውም ሙሴ የእስራኤልን ሕዝብ ባሕረ ኤርትራን ካሻገራቸው በኋላ ወደ ምድረ ርስት፤ ነፍሳት ደግሞ በክርስቶስ መሪነት ከሲኦል ወደ ገነት መግባታቸውን የሚገልጽ ነው፡፡ ዕለቱም ሙሴ የወልደ እግዚአብሔር፤ በትረ ሙሴ የመስቀል ምሳሌ፤ግብፅ የሲኦል፤ የገሃነመ እሳት፤ የፈርዖን የዲያብሎስ፤ ሠራዊቱ የሠራዊተ ዲያብሎስ፤ እስራኤል የምእመናንና ባሕረ ኤርትራ የባሕረ ሲኦል ምሳሌ ነው፡፡

ሰኞ– ማዕዶት (ፀአተ ሲኦል)

ማዕዶት የቃሉ ትርጓሜ መሻገር ሲሆን፤ በዚህ ቀን ቤተ ክርስቲያን ነፍሳት በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ከሞት ወደ ሕይወት፤ ከሐሳር ወደ ክብር፤ ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሲኦል ወደ ገነት መሻገራቸውንና ፉሲካችን ክርስቶስ መሆኑን ታስባለች።

ማክሰኞ– ቶማስ

ቅዱስ ቶማስ በጦር የተወጋ ጎኑን፤ በቀኖት የተቸነከረው እጁንና እግሩን ካላየሁ አላምንም በማለቱ ክርስቶስም «ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤እጅህንም አምጣና ወደ ጎኔ አግባ፤ እመን እንጂ ተጠራጣሪ አትሁን» ብሎታል። ቶማስም «ጌታዬ አምላኬም»፤ ብሎ በመለሰ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስም «ስለ አየኸኝ አመንህን? ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓንስ ናቸው» አለው (ዮሐ ፳፥፳፯-፳፱)፤ ቶማስ የጌታን ፍቅር ተገንዝቦ ትንሣኤውን ስላመነ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዕለቱን ቶማስ ብላ ታስበዋለች።

ዲዲሞስ የተባለ ከአሥራ አንዱ ደቀ መዛሙር አንዱ ቶማስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዝግ ቤት ገብቶ «ሰላም ለሁላችሁ ይሁን» ባላቸው ጊዜ ከእርሳቸው ጋራ አልነበረም»። ከ፲፪ቱ ሐዋርያት አንዱ (ማቴ. ፲፥፪-፫) ቶማስ በአራማይክ ዲዲሞስ በግሪክ መንታ ማለት ነው፤ (ዮሐ. ፳፥፳፬)፡፡ ቶማስ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ በፋርስና በሕንድ ወንጌልን እንዳስተማረ ይነገራል። ለቶማስ ጎኑን እንዲዳስስ የፈቀደው ለሌሎችም ቅዱሳን ሐዋርያት የተቸነከረውን እጅና እግሩን ያሳየው ካህናት ሥጋውና ደሙን እንዲፈትቱ ነው፤ ዮሐንስም በእጃችን ዳሰስነው ብሏል፤ (ሉቃ. ፳፬፥፴፱)፡፡

ለማርያም መግደላዊት ግን የተነሣ ዕለት አትንኪኝ ማለቱ ለሴቶች ሥጋውን ደሙን መፈተት አልተፈቀደም ሲል ነው ብለው ሊቃውንት ያትታሉ፤ «አትንኪኝ፤ ገና ወደ አባቴ አላረግሁምና፤ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሂጅና፡- ወደ አባቴ÷ ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬ÷ ወደ አምላካችሁም አርጋለሁ አለ ብለሽ ንገሪአቸው» አላት፤ (ዮሐ. ፳፥፲፯)። ገቦ መለኮቱን የዳሰሰች እጁ በሕይወት ትኖራለች፤ በሕንድ ሀገር ከታቦት ጋር በመንበር ላይ ትኖራለች። በየዓመቱ በእመቤታችን በዓል በአስተርእዮ ሊያጥኑ ሲገቡ የሚሾመውን ወጥታ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች፤ ዓመት አገልግሎ ያርፋል።

ረቡዕ –አልዓዛር

አልዓዛር ክርስቶስ ያስነሣው የማርያምና የማርታ ወንድም ነው፤ የስሙም ትርጓሜ እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው፤ (ዮሐ. ፲፩፥፯-፵፰)፤ አልዓዛር የሞተው መጋቢት ፲፯ ነበር፡፡ እህቶቹም ክርስቶስ እንዲመጣ መልእክት ልከውበት ነበር፤ ክርስቶስ ግን በ፬ኛው ቀን ማለትም መጋቢት ፳ መጥቶ ከሞት አስነሥቶታል፤(ዮሐ.፲፩፥፵፬)፡፡ ፋሲካውንም በወዳጁ በአልዓዛር ቤት ያከብር ዘንድ ከቀደ መዛሙርቱ ጴጥሮስንና ዮሐንስን አስቀድሞ ላከ፤ ከዚያም በአልዓዛር ቤት ሆኖ የሐዲስ ኪዳንን ሥርዓት ምሥጢረ ቁርባንን ሰርቶ ለደቀ መዛሙርቱ አሳያቸው፤ አልዓዛር ከተነሣ በኋላ በሐዋርያት ኤጲስ ቆጶስነት ተሸሞ ፵ ዓመት አገልግሎ ግንቦት ፳፯ ቀን ዐርፏል (ስንክሳር ግንቦት ፳፯)፡፡

አዳም ሐሙስ

አዳም የመጀመሪያ ሰውና የሰው ሁሉ አባት ነው፤ በ፮ኛው ቀን የተፈጠረ የሰው ሁሉ ምንጭ ስለሆነ የሰው ዘር ሁሉ ከእርሱ ተገኝቷል፡፡ በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው የተስፋ ቃል ስለመፈጸሙ፤ (ዘፍ. ፫÷፲፭) አዳም ከነልጆቹ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻ ስለመውጣቱ ይታሰብበታል፡፡ ክርስቶስ በተነሳበት በአምስተኛው ቀን ሐሙስ አዳም ይባላል፤ ጌታችን አዳምን ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ብሎ ቃል ገብቶለት እንደነበር በቀሌምንጦስ ተጽፏል፡፡

አዳምና ሔዋን በገነት ፯ ዓመት ከቆዩ በኋላ ትእዛዙን በመተላለፋቸው ከኤደን ገነት አስወጣቸው (ኩፋ.፬፥፲፮፤ዘፍ.፫፥፳፫) «ብዙ ተባዙ» ያለው ቃል እንዳይቀር በምድር ላይ ወርደው ልጆችን ወለዱ ይላል፡፡ የተወለዱትም ልጆችም በቁጥር ፷ እንደሆኑ (፩መቃ. ፳፰፥፮) የተወለዱት ልጆች ደጎችና ክፉዎች እንደ ነበሩ በአቤልና በቃየል ታውቋል፤ (ዘፍ. ፬፥፰)፤ አዳም በዚህ ዓለም ፱፻፴ ዓመት ኑሮ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በ፵፻፭፻፸ ሚያዚያ ፮ ዐርፏል፡፡

ዐርብ– ቤተ ክርስቲያን

ዐርብ የእግዚአብሔር ቅድስት ማደሪያ በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ተሰይማለች፤ ይህም ሁሉም ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የተፈጸመባት ዕለት በመሆኗ ነው፤ ዕለተ ዐርብ፤ የሥራ መከተቻ፤ ምዕራብና መግቢያ በሚሉት ስያሜዎችም ትጠራለች፡፡

በዕለቱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልዕልተ መስቀል ያደረገውን ተአምር በመስቀሉ ድኅነትን እንዳሳየ፤ በቀራንዮ የሕንጻዋ መሠረት እንደተተከለላትና ሥጋ መለኮት እንደተቆረሰላት፤ ልጆቿን ከማሕፀነ ዮርዳኖስና ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ የምትወልድበት ማየ ገቦ እንደፈሰሰላት ተገልጾባታል፤(ኤፍ.፪፥፲፱፤ራዕ.፩፥፮-፰)፡፡

ቅዳሜ– ቅዱሳት አንስት

ቅዳሜ ቅዱሳት አንስት ተብሎ ይጠራል፤ ይህም ስያሜ በስቅለት ዕለት በልቅሶና በዋይታ የሸኙትን፤(ሉቃ. ፳፫፥፳፯) በዕለተ ትንሣኤ ሽቱና አበባ ይዘው ወደ መቃብር የገሰገሱትን፤ ከሁሉም ቀድሞ ጌታችን በዕለተ ሰንበት ተነሥቶ ለተገለጸላቸው ማርያም መግደላዊት፤ የታናሹ ያዕቆብ እና የዮሳ እናት ማርያም፤ የዘብዴዎስም የልጆቹ እናት ሰሎሜንም መታሰቢያ ለማድረግ ነው፤«ከሳንምንቱ በመጀመሪያዩቱ ቀን ያዘጋጁትን ሽቶ ይዘው እጅግ ማልደው ወደ መቃብሩ ሄዱ፤ሌሎች ሴቶችም አብረዋቸው ነበሩ (ሉቃ. ፳፬ ፥ ፩ )፡፡

እሑድ– ዳግም ትንሣኤ

«ያም ከሳምንቱ የመጀመሪያው ቀን በመሸ ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ አይሁድን ስለ ፈሩ ተሰብስበው የነበሩት ቤት ደጁ ተቆልፎ ሳለ ጌታችን ኢየሱስ መጥቶ በመካከላቸው ቆመና÷«ሰላም ለእናንተ ይሁን» አላቸው፤ ማቴ.፳፥፲፱፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ተሰውሮ ከሰነበተ በኋላ በዕለተ እሑድ በዝግ ቤት እንዳሉ ዳግም ተገለጸላቸው፤ስለዚህም ዳግም ትንሣኤ ተባለ፡፡

(ምንጭ:-መዝሙረ ማኅሌት ወቅዳሴ፤ ሥርዓተ አምልኮ ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ፤ የዮሐንስ ወንጌል አንድምታ፤ ምዕ. ፳፥፳፬)

Ethiopia: the Land with an immense Literary Heritage

“Ethiopia: the Land with an immense Literary Heritage”

Expression of thoughts, actions, wars, victory, belief, etc. in written form during the classical era reveals human civilization. Ethiopia, having immense literary heritages for over two millennia, is the nation in Africa that possesses the second largest literary heritage next to Egypt. Ge‘ez (classical Ethiopic) is a language which serves as a medium for conveying this literary heritage. As a spoken language during and after the Axumite time, Ge‘ez plays a prominent role in socio-economic, and religio-cultural settings of the country. The “Garima Gospel”, which is the oldest existent codex in the Christian world (composed 4th – 6th cent. A.D.) is written in Ge‘ez. There are hundreds of thousands of manuscripts in Ethiopia composed in this language and deposited in different monastic archives of the country.

The golden age of Ge‘ez literature, as most scholars agree, is between the 14th to 18th centuries. Most of the works are translations from Greek, Syriac and mostly Arabic. There are a number of indigenous texts composed by Ethiopians and the list of the most influential authors include St. Yared, Abba Giyorgis of Gasicha, Abba Baheri, Emperor Zera Yaqob, Arke Sellus, and Retu’a Haymanot. The literary genre of Ethiopic literature is diverse including: biblical and religious texts, hagiographies, homiliaries, hymnodic and liturgical texts, prayer books, royal chronicles, esoteric traditions, linguistic narratives, etc.

The current conference is the Second International Conference of Ethiopian Church Studies, dedicated to discuss different topics under the theme: “Ge‘ez Literature and Manuscript Traditions in Ethiopia”. This conference is a continuation of the conference held in Lund (Sweden) titled “Ethiopian Ecclesiastical Heritage”, September 2-3, 2017, convened at Lund University. There are three keynote speakers in this conference and we have a privilege to have Prof. Getatchew Haile, the leading scholar on Ethiopian Studies, as one amongst them. We have received a large number of submissions but selected 13 papers. The papers cover the topics on biblical translations, the art of Ethiopic poetry (Qene), the significance of Ge‘ez hagiographies for the reconstruction of Ethiopian history, medicinal texts, Yaredic chanting book (Deggwa), the use of modern technology for manuscripts studies, etc. Now is the time to give due attention to explore and study Ethiopian literary heritages and to draw the attention of the stakeholders for preservation and conservation of Ethiopian manuscripts.

We, the organizers of the Second International Conference would like to thank all paper presenters and collaborators who made this conference possible. We are grateful for Mahibere Kidusan USA and Europe centers, and special thanks goes to Mahibere Kidusan Atlanta Sub-Center for their significant role in the process of organizing the conference.

May the Almighty God help us keep our literary heritage!

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ በሰሜን አሜሪካ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

  ቀሲስ ሳሙኤል ተስፋዬ መስከረም 23 ቀን 2011/October 3,2018                        

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ በሰሜን አሜሪካ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ ::

የግዕዝ ሥነ ጽሑፍና የብራና ቅርሶች በኢትዮጵያ”  በሚል መሪ ቃል ሁለተኛው  ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ በማኅበረ ቅዱሳን  የአሜሪካና  የአውሮፓ  ንዑሳን ማዕከላት አስተባባሪነት ከጥቅምት ፲-፲፩ ቀን ፳፻፲፩ ዓ.ም/October 20-21/2018  በሰሜን አሜሪካ፣  አትላንታ  ጆርጂያ በ 6202 Memorial Drive Stone Mountain, GA 30083  ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የዓለም አቀፍ ጥናት ጉባኤ ኮሚቴ  ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ (Ludwig Maximilian University, Munich, Germany) እና የኮሚቴ  አባልና የዐውደ ጥናቱ  አስተባባሪ ዶ/ር ፍሬሕይወት ወንድሙ (Wichita State University, USA) በጋራ  እንደገለጹልን  ለሁለተኛ ጊዜ በአሜሪካ አትላንታ ጆርጂያ ከተማ የሚካሄደው  ዓለም አቀፍ የጥናት ጉባኤ፤  የመጀመሪያው  ዓለም አቀፍ ዐውደ ጥናት ጉባኤ በማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል  አስተባባሪነት  በስዊድን  ሉንድ  ከተማ በተካሄደበት ወቅት  ከነበረው የዐውደ ጥናቱ  ፋይዳ፣ ቀጣይነትና አቅጣጫዎች በመነሳት  ሁለተኛው  ዐውደ ጥናት በሰሜን አሜሪካ  እንዲሆን መወሰኑን ገልጸዋል፡፡  በተጨማሪም የዐውደ ጥናቱ ዋነኛ ዓላማም  የኢ/ኦ/ተ/ ቤተክርስቲያንን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስተዋወቅ ፣ በርካታ ምሥጢራትን ይዘው የሚገኙ  የቤተ ክርስቲያን   ቅርሶቻችን ላይ ጥናትና ምርምር ማድረግ፣ ጥናትና ምርምር  የተደረገባቸውንም  ቅርሶች   በማወያየት ሀብቶቹ የሚጠበቁበትንና  ለተሻለ አገልግሎት የሚበቁበትን  ሁኔታ ማመቻቸት እንደሆነ ገልጸውናል፡፡

የጥናቶቹን  ይዘትና  ማቅረቢያ  ቋንቋ በተመለከተ ለኮሚቴው ተወካዮች ላቀረብነው ጥያቄ፤  ጥናቶቹ  በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የሚቀርቡ ሲሆኑ  በጉባኤው ላይ የሚቀርቡ ጥናታዊ ጽሑፎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚመለከቱ ሆነው፤ የአንድምታ  ትርጓሜ፣ገድላት፣ድርሳናት፣መልክአ መልኮች፣ቅኔ ፣ዜማ ፣የብራና ጽሑፎች  ፣የመድኃኒት ይዘት ያላቸው ጥቅልል ጽሑፎች፣በብራና ውስጥ የሚገኙ ሥዕሎችና በዚህ ዝርዝር ላይ ያልተካተቱ ሌሎች ከጉባኤው ዓላማ ጋር የሚሄዱ ርእሶችም  እንደሚቅቡ  ገልጸውልናል፡፡

 

”ጥናት አቅራቢዎቹ   በቤተክርስቲያናችን ቅርሶች ዙሪያ ጥናታዊ ምርምር የሚያካሂዱ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ዜጎች ሲሆኑ  የጥናት አጠቃሎአቸውን  ኮሚቴው ባስቀመጠው የመገምገሚያ  መስፈርት መሰረት ነጥብ በመስጠት   የተሻለ ነጥብ ያመጡት 13 ጥናቶች ለጉባኤው ሊቀርቡ ዝግጁዎች ናቸው፡፡ የተመረጡት የጽሑፍ አጠቃሎዎች በመጽሔት መልክ ታትመው በጉባኤው የሚሠራጩና በጉባኤው ላይ ቀርበው ውይይት የተደረገባቸውና መመዘኛውን የሚያሟሉ የጥናት ወረቀቶች ደግሞ  በ“የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት መጽሔት” (Journal of Ethiopian Church Studies) እንዲታተሙ ይላካሉ፡፡” ሲሉም አስተባባሪዎቹ ገልጸውልናል፡፡

የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ  አባላት13 ሲሆኑ  በአውሮፓ፣በአሜሪካና ካናዳ የሚኖሩ የማኀበረ ቅዱሳን አባላትና ደጋፊዎች የሆኑ በተለያዩ  ዩኒቨርሲቲዎች በማስተማርና ጥናትና ምርምር በማድረግ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንናቸው፡፡ በተጨማሪም  የውጭ ሃገር ዜጎች የሆኑ በኢትዮጵያ  ቤተክርስቲያን ታሪክ፣ ዜማና ብራና መጻሕፍት ላይ ምርምር እያደረጉ የሚገኙ  ምሁራን በማማከር ስራዎች እየረዱ እነደሆነም ለመረዳት ችለናል፡፡

 

በዐውደ ጥናቱ ሦስት ቁልፍ ተናጋሪዎች (Keynote Speakers) ሲኖሩ እነዚህም፡-

1.ሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴ ዓለማየሁ – የዴንቨር ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢ.ኦ.ተ. ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ ሰሜን አሜሪካ፡፡

2.ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ – ሒል ሙዚየም (HMML)፣ ኮሌጅቪል፤ ሰሜን አሜሪካ፡፡

3.ፕሮፌሰር ስቲቭ ዴላማርተር – ጆርጅ  ፎክስ ዩኒቨርሲቲ፣  ሰሜን አሜሪካ  መሆናቸው ተገልጿል፡፡

 

 

በኢትዮ ሶማሌ ሀገረ ስብከት በተፈጸመው ኢ- ሰብአዊ ድርጊት ለተቃጠሉት አብያተ ክርስቲያናት፣ ለተጐዱት ካህናትና ምእመናንን መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው የድጋፍ ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ

ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ

በኢትዮ ሶማሌ ሀገረ ስብከት በተፈጸመው ኢ- ሰብአዊ ድርጊት ለተቃጠሉት አብያተ ክርስቲያናት፣ ለተጐዱት ካህናትና ምእመናንን መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው የድጋፍ ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠየቀ፡፡

በተከሰተው ግርግርና ግጭት አብያተ ክርስቲያናት መቃጠላቸው፤ ካህናትና ምእመናን መገደላቸው፤ ንዋየ ቅድሳት መዘረፋቸውና የአብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችና ምእመናን ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሰደዳቸው በተለያዩ መገናኛ ብዙኅን የተገለጸ ሲሆን እስካሁን የተደረገው ድጋፍ ከደረሰው ጉዳት አንጻር ዝቅተኛ በመሆኑ ድጋፉ ላይ ምእመናን ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባቸው ተገልጿል፡፡ Read more