ዘመነ ስብከት

በኩረ ፍሥሐ ቀሲስ ኃይለኢየሱስ ተመስገን

ዘመነ ስብከት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ከሁሉ አስቀድሞ ሃይማኖትን መመስከር እንዲገባ ቅድመ ዓለም ከእግዚአብሔር አብ ያለ እናት፣ አካል ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ የተወለደ፣ ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው አካላዊ ቃል ፤ ድኀረ ዓለም ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያለ አባት፣ መለወጥ ሳያገኛት ዘር ምክንያት ሳይሆን፣ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው የሆነ ፤ ወልደ እግዚአብሔር በመለኮቱ ወልደ ማርያም በትስብእቱ ፤ የሚባል ጌታ በተዋሕዶ ከበረ ብለን የቀናች የአባቶቻችን ሃይማኖታቸው ተዋሕዶን እንመሰክራለን፡፡

ስንዱዋ እመቤት ቤተክርስቲያናችን ወራትን እና ዘመናትን ከፍላ ነገረ ሃይማኖትን ታስተምራለች።አባቶቻችንም የወራቱንና የቀናቱን  የሰንበታቱንም ምስጢር በማገናዘብ የመጽሐፍ ቅዱስን ምንባባት ከቅዱስ ያሬድ መዝሙር ጋር በማዛመድ ግጻዌ የሚባልን መጽሐፍ ሰርተውልናል።

አባቶቻችን ሊቃውንት ከኅዳር ፮  እስከ  ስብከት  ያለውን ንዑስ ዘመን  ዘመነ አስተምህሮ ይሉታል፡፡ ስብከት የሚውለው ከታኅሣሥ ፯ እስከ  ፲፫  ባሉት ቀናት ውስጥ በሚውለው እሁድ በመሆኑ ፤ ዘመነ አስተምህሮ ዝቅ ብሎ  ከኅዳር ፮ እስከ ታኅሣሥ ፯  ወይም ከፍ ብሎ  ከኅዳር ፮  እስከ  ታኅሣሥ ፲፫ ያለውን ጊዜ ያጠቃልላል፡፡

ዘመነ አስተምህሮ ከዘመነ ስብከት መቅደሙ እግዚአብሔር አዳምን ይቅር እንዳለው ለማጠየቅ ሲሆን፣ ከዘመነ አስተምህሮ ቀጥሎ ዘመነ ስብከት መባሉ ደግሞ አዳምን ይቅር ያለው ንጉሠ ሰማይ ወምድር እግዚአብሔር አምላክ ሰው ሁኖ የሚወለድበት ዘመን እንደ ደረሰ ለማጠየቅ ነው፡፡

 

ስብከት ኢይወርዱ ታኅሣሥ ሰባት ሲሆን ኢየዐርጉ ደግሞ ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ስለሆነ ከታኅሣሥ ሰባት እስከ ታኅሣሥ ዐሥራ ሦስት ባለው ይመላለሳል ፡፡

በዚህም ዕለተ ሰንበት  ሙሴ በኦሪት፥ ነቢያትም ስለ እርሱ ስለጻፉለት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስጋዌ ትንቢቱን አውቆ ያናገረ ምሳሌውን ያስመሰለ ነቢያት አስቀድመው ከወዲያ ዓለም ወደዚህ ዓለም እንደሚመጣ ሰው ሆኖ  እንደሚያድነን ትንቢት መናገራቸውን ሱባኤ መቁጠራቸውን የሚነገርበት የሚሰበክበት በመሆኑ ስብከት ይባላል።

አባቶቻችን ስብከት የሚውልበትን ቀን የሚያሰሉት በወርኀ ታኅሣሥ መባቻ ፣ በነቢየ እግዚአብሔር በኤልያስ ክበረ በዓል ነው፡፡ የባህረ ሐሳቡን ትምህርት በመያዝ በቀላሉ ለማስታወስ ጥንተ ቀመርን ወይም የዕለታት ተውሳክን በመጠቀም ማስላት እንችላለን፡፡

ጥንተ ቀመርን በመጠቀም ስናሰላ

 

ስብከት ታኅሣሥ ፲፫ የሚሆነው ኤልያስ(ታኅሣሥ መባቻ)  በጥንተ ቀመር (በዕለተ ማክሰኞ)  የዋለ እንደሆነ ነው፡፡በዚህም መሰረት፦

  1. ታኅሣሥ 1 ማክሰኞ ከዋለ ፣ ስብከት ታኅሣሥ 13 ቀን ይውላል፡፡
    2. ታኅሣሥ 1 ረቡዕ ከዋለ ፣  ስብከት ታኅሣሥ 12 ቀን ይውላል፡፡
    3. ታኅሣሥ 1 ሐሙስ ከዋለ፣ ስብከት ታኅሣሥ 11 ቀን ይውላል፡፡
    4. ታኅሣሥ 1 አርብ ከዋለ ፣ስብከት ታኅሣሥ 10 ቀን ይውላል፡፡
    5. ታኅሣሥ 1 ቅዳሜ ከዋለ፣ ስብከት ታኅሣሥ 9 ቀን ይውላል፡፡
    6. ታኅሣሥ 1 እሑድ ከዋለ፣ ስብከት ታኅሣሥ 8 ቀን ይውላል፡፡

7.ታኅሣሥ 1 ሰኞ ከዋለ፣ ስብከት ታኅሣሥ 7 ቀን ይውላል፡፡

የዕለታት ተውሳክን በመጠቀም ስናሰላ

 

የዕለታት ተውሳክ በቅዳሜ ይጀምራል እርሱም ፰ ነው ፡፡ ቅዳሜ(8) ፣ እሁድ(7) ፣  ሰኞ(6) ፣ ማክሰኞ(5) ፣ ረቡዕ(4) ፣ ሃሙስ(3) ፣ ዓርብ(2)

በዚህም መሰረት፦

1.ታኅሣሥ 1 ቅዳሜ ከዋለ፣ ስብከት (1+8=9) ታኅሣሥ 9  ቀን ይውላል፡፡

2.ታኅሣሥ 1 እሑድ ከዋለ፣ ስብከት (1+7=8) ታኅሣሥ 8  ቀን ይውላል፡፡
3.ታኅሣሥ 1 ሰኞ ከዋለ፣ ስብከት (1+6=7) ታኅሣሥ 7 ቀን ይውላል፡፡
4.ታኅሣሥ 1 ማክሰኞ ከዋለ ፣ ስብከት (1+5=6 ይሆናል።ሰባት ስላልሞላ ሌላ ሳምንት ይፈልጋል ስለዚህ  6+7=13 ) ታኅሣሥ 13 ቀን ይውላል፡፡
5. ታኅሣሥ 1 ረቡዕ ከዋለ ፣  ስብከት (1+4+7=12) ታኅሣሥ 12 ቀን ይውላል፡፡
6. ታኅሣሥ 1 ሐሙስ ከዋለ፣ ስብከት(1+3+7=11)  ታኅሣሥ 11 ቀን ይውላል፡፡
7. ታኅሣሥ 1 አርብ ከዋለ ፣ስብከት (1+2+7) ታኅሣሥ 10 ቀን ይውላል፡፡

 

ምስባክ ዘስብከት መዝ ፻፵፫፥፯


‹‹ፈኑ እዴከ እምአርያም ፤

አድኅነኒ ወባልሐኒ እማይ ብዙኅ፤

ወእምእዴሆሙ ለደቂቀ  ነኪር ። ››

 

በስብከት (ከታኅሣሥ ፯ እስከ  ፲፫  ባሉት ቀናት ውስጥ በሚውለው እሁድ) ነቢያት የጌታን ሥጋዌ ማስተማራቸው ይነገርበታል ፡፡ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ልጅነቱን ካጣ ከገነት ከወጣ በኋላ ‹‹እግዚአብሔርን ያህል ጌታ ገነትን ያህል ቦታ በኃጢአቴ ምክንያት አጣው›› እያለ ሲያዝን ጌታ ኀዘኑን አይቶ ጸሎቱን ሰምቶ ‹‹ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅ ተወልጄ አድንኃለው›› ብሎ ተስፋ ሰጥቶታል፡፡  ከእሱ በኋላ የተነሱ ነቢያት በግዝረታቸው፣ በመስዋዕታቸው መዳን የማይቻላቸው ቢሆን ለአዳም በሰጠው ተስፋ ከሰማያት ወርዶ፣ ከድንግል ተወልዶ፣ በሕማሙ በሞቱ ያድናቸው ዘንድ ‹‹ፈኑ እዴከ እምአርያም  እጅህን ከአርያም ላክ አድነኝም››  እያሉ ተማጽነውታል፡፡

 

ፈኑ እዴከ እምአርያም

 

እድ መዝራዕት የሚባል ልጅህን በሥጋ ላክ አንድም ረድኤትህን ከአርያም ላክ፤ኢየሱስ ክርስቶስን እዱ መዝራዕቱ ለአብ ይለዋል።የሰው ኀይሉ በክንዱ እንዲታወቅ የአብም ኀይሉ በውልድ ይታወቃልና አንድም ክንድ ከአካል ሳይለይ የወደቀውን ዕቃ አንስቶ ይመለሳል እርሱም ከአብ አንድነት ሳይለይ አዳምን ያድናልና አድኗልና እንድም በክንድ የራቀውን ያቀርቡበታል የቀረበውን ያርቁበታል በርሱም ጻድቃንን ንዑ ኀቤየ ብሎ ያቀርብባታል ኃጥአንን ሑሩ እምኔየ ብሎ ያርቅበታልና ነው።

 

አድኅነኒ ወባልሐኒ እማይ ብዙኅ

 

በሥልጣንህ ከብዙ መከራ ከብዙ ጦር አድነኝ ፤አንድም በልጅህ ከፍትወታት እኩያት ከኀጣውእ ከፍዳ ከመከራ ነፍስ ፈጽመህ አድነኝ።

ወእምእዴሆሙ ለደቂቀ  ነኪር

 

ከዲያቢሎስ ወገኖች ሥልጣን አድነኝ አንድም ከባዕድ ልጆች እጅ አድነኝ።
ሀብተ ትንቢት የተሰጠው ቅዱስ ዳዊት የጌታን ልደት በተስፍ ተመልክቶ ከዚህም በተጨማሪ ሌሎችን ትንቢቶች ተናግሯል።

 

በስብከት የሚነበቡ ምንባባት

 

በስብከት የሚነበቡ ምንባባት በዕለቱ መዝሙር ‹‹ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ…››ከዓለም በፊት የነበረውንና መድኃኒት የሆነውን ወልድን እንሰብካለን በሚለው የቅዱስ ያሬድ ዜማ ተስማምተው የተዘጋጁ ናቸው።

 

በዚህ ዕለት የሚነበቡት ምንባባት፥ ነቢያት ሱባኤ እየገቡ ምሥጢር እየተገለፀላቸው ስለ ነገረ ሥጋዌው ትንቢትና በብዙ ምሳሌ መናገራቸውን እንዲሁም   ተስፋ ትንቢታቸው በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መፈጸሙን የሚያስረዱ ናቸው።

 

    • ዕብ ፩፥፩-፲፬ ‹‹ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ አይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ ፥ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን፤እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ….››

 

  • ፪ኛ ጴጥ ፫ ፥ ፩፡፲ ‹‹ወዳጆች ሆይ፥ አሁን የምጽፍላችሁ መልእክት ይህች ሁለተኛይቱ ናት። በቅዱሳን ነቢያትም ቀድሞ የተባለውን ቃል በሐዋርያቶቻችሁም ያገኛችኋትን የጌታንና የመድኃኒትን ትእዛዝ እንድታስቡ በሁለቱ እያሳሰብኋችሁ ቅን ልቡናችሁን አነቃቃለሁ።በመጨረሻው ዘመን እንደ ራሳቸው ምኞት የሚመላለሱ ዘባቾች በመዘበት እንዲመጡ ይህን በፊት እወቁ፤እነርሱም  የመምጣቱ የተስፋ ቃል ወዴት ነው፧ አባቶች ከሞቱባት ጊዜ፥ ከፍጥረት መጀመሪያ ይዞ ሁሉ እንዳለ ይኖራልና ይላሉ።….››

 

  • የሐዋ ፫ ፥ ፲፯ ፡ ፳፮ ‹‹አሁንም፥ ወንድሞቼ ሆይ፥ እናንተ እንደ አለቆቻችሁ ደግሞ ባለማወቅ እንዳደረጋችሁት አውቄአለሁ፤እግዚአብሔር ግን ክርስቶስ መከራ እንዲቀበል አስቀድሞ በነቢያት ሁሉ አፍ የተናገረውን እንዲሁ ፈጸመው።እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።እግዚአብሔር ከጥንት ጀምሮ በቅዱሳን ነቢያቱ አፍ የተናገረው፥ ነገር ሁሉ እስከሚታደስበት ዘመን ድረስ ሰማይ ይቀበለው ዘንድ ይገባልና።ሙሴም ለአባቶች። ጌታ አምላክ እኔን እንዳስነሣኝ ነቢይን ከወንድሞቻችሁ ያስነሣላችኋል፤ በሚነግራችሁ ሁሉ እርሱን ስሙት።ያንም ነቢይ የማትሰማው ነፍስ ሁሉ ከሕዝብ ተለይታ ትጠፋለች አለ።ሁለተኛም ከሳሙኤል ጀምሮ ከእርሱም በኋላ የተናገሩት ነቢያት ሁሉ ደግሞ ስለዚህ ወራት ተናገሩ።እናንተ የነቢያት ልጆችና እግዚአብሔር ለአብርሃም። በዘርህ የምድር ወገኖች ሁሉ ይባረካሉ ብሎ፥ ከአባቶቻችን ጋር ያደረገው የኪዳን ልጆች ናችሁ።ለእናንተ አስቀድሞ እግዚአብሔር ብላቴናውን አስነሥቶ፥ እያንዳንዳችሁን ከክፋታችሁ እየመለሰ ይባርካችሁ ዘንድ፥ ሰደደው።››

 

 

 

ወንጌል ዘስብከት ዮሐ ፩፥፵፬፡፶፪

 

‹‹በነገው ኢየሱስ ወደ ገሊላ ሊወጣ ወደደ፥ ፊልጶስንም አገኘና ተከተለኝ አለው። ፊልጶስም ከእንድርያስና ከጴጥሮስ ከተማ ከቤተ ሳይዳ ነበረ። ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው።

ናትናኤልም ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን አለው። ፊልጶስ መጥተህ እይ አለው።ኢየሱስ ናትናኤልን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ ስለ እርሱ ተንኰል የሌለበት በእውነት የእስራኤል ሰው እነሆ አለ።

ናትናኤልም ከወዴት ታውቀኛለህ አለው። ኢየሱስም መልሶ ፊልጶስ ሳይጠራህ፥ ከበለስ በታች ሳለህ፥ አየሁህ አለው።

ናትናኤልም መልሶ መምህር ሆይ፥ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፤ አንተ የእስራኤል ንጉሥ ነህ አለው።

ኢየሱስም መልሶ ከበለስ በታች አየሁህ ስላልሁህ አመንህን ከዚህ የሚበልጥ ነገር ታያለህ አለው።እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው።››

 

በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል  እንደምንረዳው ፊሊጶስ ናትናኤልን እንደጠራውና ፤ናትናኤልን ፊሊጶስ ሳይጠራው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስቀድሞ ናትናኤልን  እንደሚያውቀው፤ ስለእርሱም ደግነት መናገሩን እናያለን።

አባቶቻችን ፊሊጶስ ሳይጠራህ በፊት ከበለስ በታች ሳለህ አየሁህ የሚለውን በአንድምታ ትርጓሜ አስቀምጠውልናል

  • በቅትለተ ሕጻናት ሄሮድስ ሕጻናቱን ሲያስፈጅ እናቱ በቀፎ አድርጋ ከበለስ ሥር ሠውራው ነበርና ያንጊዜ ያዳንኩህ እኔ ነኝ ሲል ነው
  • ሰው ገድሎ አስቀብሮ ነበርና አንድም  የጎልማሳ ሚስት ቀምቶ የማይገባ ሥራ ሲሰራ ነበርና አውቅብሀለሁ ሲለው ነው
  • ባለጸጋ ነው ከዚያ ሆኖ ወይፋፍን ሲያስፈትን ፈረስ በቅሎ ሲያሰግር ይውል ነበርና አውቅሀለሁ ሲለው ነው
  • ምሑረ ኦሪት ነው ከዚያ ሆኖ የተነገረው ትንቢት ደረሰ የተቆጠረው ሱባኤ ቀረ እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ ይውል ነበርና አውቅልሃለሁ ሲለው ነው።
  • የበለስ ቅጠሉ ሰፊ እንደሆነ ኃጢአት ሰፍናብህ አየሁህ ሲለው ነው።

በዚህም የስብከትና የትምህርት ዕለት ነገረ ሥጋዌው እና የነቢያት ውረድ ተወለድ አድኅነን የሚል ጸሎትና ልመና በሚታሰብበት ሰንበት ፤ ሁላችንም እራሳችን በቃለ እግዚአብሔር መክረን የአምላካችን ውለታ ማሰብ ያስፈልገናል።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 

The Message of the Holy Cross

The Message of the Holy Cross

Alemayehu Desta

“For the preaching of the cross is to them that perish foolishness, but unto us which are saved,
it is the power of God.” /1 Corinthians 1:18/

Our Lord and Savior Jesus Christ redeemed us by suffering and giving us His life for us on the Holy Cross. The Holy Cross is an instrument of our salvation. After the Crucifixion of Jesus Christ, His crucifiers buried the Holy Cross under a pile of dirt so that many would not become Christians because of the miracles manifested by it.

The mother of Emperor Constantine, Queen Helena travelled to Jerusalem to find the Holy Cross. After a long search and prayer, she was advised by a righteous man in Jerusalem, Kyriakos to light a bonfire with incense. On the 16th day of the Ethiopian month, Meskerem, Queen Helena burnt a bonfire as advised, and the smoke from the burning pile of branches with incense went up and descended to the place where the Holy Cross was buried.

We celebrate the founding of the Holy Cross by lighting bonfire with prayer to commemorate the founding of the Holy Cross every year on the 16th day of the first Ethiopian month–Meskerem (September 26).  The right half of the Cross later come to Ethiopia and rests at Gishen Mariam, a mountain with the shape of a cross.

Why do we venerate sign of the Cross?

The Romans in the early century used to punish anyone condemned to death on a cross. But, because our Lord and Savior Jesus Christ redeemed us by on a cross, this symbol of death became a symbol of life and love.

The Holy Cross is a sign of our salvation: During their exodus from Egypt to Jerusalem, the Israelites used to disobey the Lord God often. Once, the Lord God sent a venomous serpent among them, and many died of the serpent’s bite. They pleaded with Moses to pray for them, and after Moses’ prayer, the Lord God commanded him to make a serpent from a brass and hang it on a pole. The Lord God said that whoever was bitten by the venomous serpent, would be healed if he/she looked at this brass serpent on a pole. /Numbers 21/. Likewise, when we focus on the Holy Cross, we see the crucified Jesus Christ who gave up His life so that we can have eternal life. It is on the Cross that we were redeemed from our sins and from death.

The Holy Cross is a sign of love: Our Lord Jesus Christ said that there is no greater love than giving one’s life for another. He showed us that ultimate love by giving His life on the Cross for our sake. It was not because He was powerless that He was crucified, but it is because He loved us that He willingly endured unimaginable pain and suffering on the Cross. The hatred of his crucifiers, the pain and affliction He endured was intolerable, but He tolerated all that because He loved us, including those who crucified Him.

The Cross is a sign of the Power of God: The Lord’s crucifiers considered it a weakness when the Lord Jesus Christ accepted every act of hatred without resistance and with silence. But, in their hatred, they failed to see the power of God manifested on the cross:

o   He was silent on the Cross, but powerful, for His love was enduring and it spoke much more than words could explain. The Prophet Isaiah spoke of His silence in his prophecy saying, “He was oppressed and He was afflicted, yet He opened not His mouth.” /Isaiah 53:7/

  • Surrounded by hatred, His love was powerful even on the Cross: Those who crucified our Lord Jesus Christ mocked Him saying He could save others, but could not save Himself. But He was Powerful in His love, for His Crucifixion on the Cross was a result of His redeeming love. No one had the power to crucify Him, if He was not willing to give up Himself for our salvation.

o   In His affliction, He was powerful for every pain He endured was redemption for all our transgressions. His hands were nailed to the Cross to pay for the hands of Adam and Eve that picked the forbidden fruit. His feet were nailed to the Cross to pay for their transgression in walking to commit sin. He put in His mouth a mixture of vinegar and gall to pay for their mouth that ate the forbidden fruit.

o   With His hands nailed to the Cross, He looked weak and vulnerable, but He was powerful for those outstretched hands are calling us and drawing us to Him. “I have spread out my hands all the day unto a rebellious people, who walk in a way that was not good, after their own thoughts.” /Isaiah 65:2/

  • The devil thought that The Lord on the Cross was merely a man no different from any criminal who was condemned to die on a cross in the past. However, he quickly learned that he was wrong when he  was seized by the power of the Lord Jesus Christ as he approached Him to take away His soul to Hades just the way he did with all mankind since the fall of Adam and Eve until this day.
  • The power of the Lord Jesus Christ was disguised from the devil and his crucifiers, yet, the criminal crucified to the right of the Lord Jesus Christ was able to see it and asked for forgiveness and for the Lord to remember him in His Kingdom. Our Lord Jesus Christ said to him, “Today you will be with me in paradise.” /Luke 23:43/

 

The Cross is a sign of discipleship: Our Lord fulfilled the work of our redemption on the Holy Cross, but we are also called into a life of discipleship by this sign of the Cross. Our Lord Jesus Christ said, “If any man will come after me, let him deny himself and take up his cross, and follow me.” /Matthew 16:24/

The Holy Cross is an integral instrument of our salvation and it is a sign of the love, and power of God, and of our salvation. Therefore we bear the sign of the cross in our daily life and in our life of worship. For we are called to follow Christ bearing the cross.