በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል የኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ 2ተኛውን ሐዊረ ሕይወት በተሳካ ሁኔታ አካሄደ

በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል  የኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ 2ተኛውን ሐዊረ ሕይወት በተሳካ ሁኔታ አካሄደ::

ግንኙነት ጣቢያው መነሻውን ከኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በማድረግ ኦሃዮ ኮሎምበስ ወደሚገኘው የደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ፣ ጥቅምት 10 ቀን 2011 ዓ. ም በኢንዲያና ዙሪያ የሚገኙ ከ70 በላይ ምዕመናንን ያሳተፈ መንፈሳዊ ጉዞ አካሂዷል።

የጉዞው ተሳታፊዎች በደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቅጽር መገኘት የጀመሩት ከጠዋቱ 6:00 AM ሰዓት ቀደም ብለው ሲሆን ሁሉም ተሳታፊዎች በየተመደቡበት አውቶብስ ወይም ቫን መሳፈራቸው እንደተረጋገጠ በኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ንጉሤ ጸሎት ከተደረገ በኋላ ጉዞው ተጀምሯል። 3 ሰዓታት በፈጀው ጉዞ ተጓዦቹን በሐዋርያትና በቅዱሳን ስም በቡድን በመመደብ የመንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር እንዲያደርጉ የተደረገ ሲሆን በጉዞው መጀመሪያና መጨረሻ በጋራ በመዘመር ጉዞው ልዩ መንፈሳዊ ድባብ እንዲኖረው ሆኗል።

ተጉዋዦቹ ኦሃዮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ሲደርሱ በደብሩ ካህናትና ምዕመናን አቀባበል ከተደረገላቸው በኋላ መርሐ ግብሩ በካናቱ መሪነት በጸሎት ተከፍቷል። በመቀጠልም የቁርስ መስተንግዶ በደብሩ ምዕመናን ተደርጎ ለእለቱ የተዘጋጁት መርሐ ግብራት  ቀጥለዋል። በእለቱ መልአከ አርያም ቀሲስ ብርሃኑ ጎበና መስማትንስ ስላንተ ቀድሞ በጆሮዬ ሰምቼ ነበር፤ አሁን ግን ዓይኔ አየችህ በሚል ኃይለ ቃል መነሻነት እንዲሁም የደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ያሬድ ገብረ መድኅን ንሥሐ  በሚል ርዕስ ትምህርተ ወንጌል የሰጡ ሲሆን ጸሐፌ ትዕዛዝ መምህር ታዴዎስ ግርማ ደግሞ ሰፊ የዝማሬ አገልግሎት ሰጥተዋል ። እንዲሁም ከምዕመናን ለተነሱ ጥያቄዎች በመምህራኑ ምላሽ ተሰጥቷል።

በእለቱ የኢንዲያና ደብረ ሰላም  ቅዱስ ሚካኤል እና ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል አብያተ ክርስቲያናት ሰንበት ትምህርት ቤቶች በጋራ መዝሙራትን ያቀረቡ ሲሆን ሦስት ታዳጊ ልጆች ደግሞ አባታችን በሰማያት ላይ ያለህ የሚለውን የበገና መዝሙር በጋራ አቅርበዋል።

በጉባኤው ከቀረቡት መርሐ ግብራት  የተሳታፊቹን ልዩ ትኩረት ያገኘው ዶ/ር በላይነህና ዲ/ን ፍሥሐ ያቀረቡት በማኅበረ  ቅዱሳን  ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ የሐዋርያዊ  አገልግሎት ማስፋፊያ ዋና ክፍል የተዘጋጀውን የአዳ አማንያን ጥምቀት ሪፖርት ፈተናዎችና  ቀጣይ ሥራዎች  የተመለከተ በቪዲዮ የታገዘ ገለጻ ሲሆን በተሳታፊዎቹ ዘንድ ከፍተኛ ቁጭትን አሳድሯል። እንዲሁም የተወሰኑ ምዕመናንም ይህን እንቅስቃሴ ለመደገፍ ቃል እንዲገቡ ምክንያት ሆኗል።

በኢንዲያናና አካባቢው የሚገኙ ምዕመናን ሰፊ ትምህርተ ወንጌል እንዲያገኙ ፣ ከተዘጋጀው የምክረ አበው እና ሰፊ የዝማሬ አገልግሎት በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲበረቱ እንዲሁም ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲያገኙ ታስቦ በተዘጋጀው በዚህ ሐዊረ ሕይወት የተሳተፉት ምዕመናን በመንፈሳዊ ጉዞው መደሰታቸውን ገልጸዋል። እንዲሁም ለኦሃዮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን $1,156.00 ዶላር መብዐ ሰብስበው ሰጥተዋል።

ለሐዊረ ሕይወቱ መሳካት የኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ምዕመናንን በመቀስቀስ ፣ የትራንስፖርትና የመሳሰሉትን ለጉዞ አስፈላጊ ነገሮች በማፈላለግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረጉ ሲሆን የኦሃዮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንም እንዲሁ ከአስተዳዳሪው ጀምሮ ሰበካ ጉባኤውና ምዕመናንኑ ለተጓዦቹ የቁርስና ምሳ መስተንዶ በማድረግ ፣ በደብሩ የተጋጀውን የ2011ዓ.ም ቀን መቁጠሪያ በነጻ በማደል እንዲሁም መርሐ ግብሩ የተሳካ እንዲሆን አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

በመጨረሻም ተጉዋዦቹን መርተው የሄዱት የኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ንጉሤ ገብሬ ለሐዊረ ሕይወት አስተባባሪዎቹ የማኅበረ ቅዱሳን ኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ ፣ ለአስተናጋጁ ደብር ኦሃዮ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፣ ለሁለቱ ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በጉባኤው ላይ ለተገኙት ካህናት መዘምራን እና ምዕመናን ምስጋና አቅርበዋል። የማኅበረ ቅዱሳን ኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ ሰብሳቢ ዶ/ር ዓለማየሁ በበኩላቸው ለጉዞው መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉት ካህናት ፣ አድባራት ፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ተሳታፊ ምዕመናን ምስጋና አቅርበው መርሐ ግብሩ 5፡30 PM ላይ በጸሎት ተደምድሟል። ተጉዋዦቹም እየዘመሩ ወደ ኢንዲያና በሰላም ተመልሰዋል።

Ethiopia: the Land with an immense Literary Heritage

“Ethiopia: the Land with an immense Literary Heritage”

Expression of thoughts, actions, wars, victory, belief, etc. in written form during the classical era reveals human civilization. Ethiopia, having immense literary heritages for over two millennia, is the nation in Africa that possesses the second largest literary heritage next to Egypt. Ge‘ez (classical Ethiopic) is a language which serves as a medium for conveying this literary heritage. As a spoken language during and after the Axumite time, Ge‘ez plays a prominent role in socio-economic, and religio-cultural settings of the country. The “Garima Gospel”, which is the oldest existent codex in the Christian world (composed 4th – 6th cent. A.D.) is written in Ge‘ez. There are hundreds of thousands of manuscripts in Ethiopia composed in this language and deposited in different monastic archives of the country.

The golden age of Ge‘ez literature, as most scholars agree, is between the 14th to 18th centuries. Most of the works are translations from Greek, Syriac and mostly Arabic. There are a number of indigenous texts composed by Ethiopians and the list of the most influential authors include St. Yared, Abba Giyorgis of Gasicha, Abba Baheri, Emperor Zera Yaqob, Arke Sellus, and Retu’a Haymanot. The literary genre of Ethiopic literature is diverse including: biblical and religious texts, hagiographies, homiliaries, hymnodic and liturgical texts, prayer books, royal chronicles, esoteric traditions, linguistic narratives, etc.

The current conference is the Second International Conference of Ethiopian Church Studies, dedicated to discuss different topics under the theme: “Ge‘ez Literature and Manuscript Traditions in Ethiopia”. This conference is a continuation of the conference held in Lund (Sweden) titled “Ethiopian Ecclesiastical Heritage”, September 2-3, 2017, convened at Lund University. There are three keynote speakers in this conference and we have a privilege to have Prof. Getatchew Haile, the leading scholar on Ethiopian Studies, as one amongst them. We have received a large number of submissions but selected 13 papers. The papers cover the topics on biblical translations, the art of Ethiopic poetry (Qene), the significance of Ge‘ez hagiographies for the reconstruction of Ethiopian history, medicinal texts, Yaredic chanting book (Deggwa), the use of modern technology for manuscripts studies, etc. Now is the time to give due attention to explore and study Ethiopian literary heritages and to draw the attention of the stakeholders for preservation and conservation of Ethiopian manuscripts.

We, the organizers of the Second International Conference would like to thank all paper presenters and collaborators who made this conference possible. We are grateful for Mahibere Kidusan USA and Europe centers, and special thanks goes to Mahibere Kidusan Atlanta Sub-Center for their significant role in the process of organizing the conference.

May the Almighty God help us keep our literary heritage!

The Message of the Holy Cross

The Message of the Holy Cross

Alemayehu Desta

“For the preaching of the cross is to them that perish foolishness, but unto us which are saved,
it is the power of God.” /1 Corinthians 1:18/

Our Lord and Savior Jesus Christ redeemed us by suffering and giving us His life for us on the Holy Cross. The Holy Cross is an instrument of our salvation. After the Crucifixion of Jesus Christ, His crucifiers buried the Holy Cross under a pile of dirt so that many would not become Christians because of the miracles manifested by it.

The mother of Emperor Constantine, Queen Helena travelled to Jerusalem to find the Holy Cross. After a long search and prayer, she was advised by a righteous man in Jerusalem, Kyriakos to light a bonfire with incense. On the 16th day of the Ethiopian month, Meskerem, Queen Helena burnt a bonfire as advised, and the smoke from the burning pile of branches with incense went up and descended to the place where the Holy Cross was buried.

We celebrate the founding of the Holy Cross by lighting bonfire with prayer to commemorate the founding of the Holy Cross every year on the 16th day of the first Ethiopian month–Meskerem (September 26).  The right half of the Cross later come to Ethiopia and rests at Gishen Mariam, a mountain with the shape of a cross.

Why do we venerate sign of the Cross?

The Romans in the early century used to punish anyone condemned to death on a cross. But, because our Lord and Savior Jesus Christ redeemed us by on a cross, this symbol of death became a symbol of life and love.

The Holy Cross is a sign of our salvation: During their exodus from Egypt to Jerusalem, the Israelites used to disobey the Lord God often. Once, the Lord God sent a venomous serpent among them, and many died of the serpent’s bite. They pleaded with Moses to pray for them, and after Moses’ prayer, the Lord God commanded him to make a serpent from a brass and hang it on a pole. The Lord God said that whoever was bitten by the venomous serpent, would be healed if he/she looked at this brass serpent on a pole. /Numbers 21/. Likewise, when we focus on the Holy Cross, we see the crucified Jesus Christ who gave up His life so that we can have eternal life. It is on the Cross that we were redeemed from our sins and from death.

The Holy Cross is a sign of love: Our Lord Jesus Christ said that there is no greater love than giving one’s life for another. He showed us that ultimate love by giving His life on the Cross for our sake. It was not because He was powerless that He was crucified, but it is because He loved us that He willingly endured unimaginable pain and suffering on the Cross. The hatred of his crucifiers, the pain and affliction He endured was intolerable, but He tolerated all that because He loved us, including those who crucified Him.

The Cross is a sign of the Power of God: The Lord’s crucifiers considered it a weakness when the Lord Jesus Christ accepted every act of hatred without resistance and with silence. But, in their hatred, they failed to see the power of God manifested on the cross:

o   He was silent on the Cross, but powerful, for His love was enduring and it spoke much more than words could explain. The Prophet Isaiah spoke of His silence in his prophecy saying, “He was oppressed and He was afflicted, yet He opened not His mouth.” /Isaiah 53:7/

  • Surrounded by hatred, His love was powerful even on the Cross: Those who crucified our Lord Jesus Christ mocked Him saying He could save others, but could not save Himself. But He was Powerful in His love, for His Crucifixion on the Cross was a result of His redeeming love. No one had the power to crucify Him, if He was not willing to give up Himself for our salvation.

o   In His affliction, He was powerful for every pain He endured was redemption for all our transgressions. His hands were nailed to the Cross to pay for the hands of Adam and Eve that picked the forbidden fruit. His feet were nailed to the Cross to pay for their transgression in walking to commit sin. He put in His mouth a mixture of vinegar and gall to pay for their mouth that ate the forbidden fruit.

o   With His hands nailed to the Cross, He looked weak and vulnerable, but He was powerful for those outstretched hands are calling us and drawing us to Him. “I have spread out my hands all the day unto a rebellious people, who walk in a way that was not good, after their own thoughts.” /Isaiah 65:2/

  • The devil thought that The Lord on the Cross was merely a man no different from any criminal who was condemned to die on a cross in the past. However, he quickly learned that he was wrong when he  was seized by the power of the Lord Jesus Christ as he approached Him to take away His soul to Hades just the way he did with all mankind since the fall of Adam and Eve until this day.
  • The power of the Lord Jesus Christ was disguised from the devil and his crucifiers, yet, the criminal crucified to the right of the Lord Jesus Christ was able to see it and asked for forgiveness and for the Lord to remember him in His Kingdom. Our Lord Jesus Christ said to him, “Today you will be with me in paradise.” /Luke 23:43/

 

The Cross is a sign of discipleship: Our Lord fulfilled the work of our redemption on the Holy Cross, but we are also called into a life of discipleship by this sign of the Cross. Our Lord Jesus Christ said, “If any man will come after me, let him deny himself and take up his cross, and follow me.” /Matthew 16:24/

The Holy Cross is an integral instrument of our salvation and it is a sign of the love, and power of God, and of our salvation. Therefore we bear the sign of the cross in our daily life and in our life of worship. For we are called to follow Christ bearing the cross.

 

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ በሰሜን አሜሪካ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

  ቀሲስ ሳሙኤል ተስፋዬ መስከረም 23 ቀን 2011/October 3,2018                        

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ በሰሜን አሜሪካ ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ ::

የግዕዝ ሥነ ጽሑፍና የብራና ቅርሶች በኢትዮጵያ”  በሚል መሪ ቃል ሁለተኛው  ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት ጉባኤ በማኅበረ ቅዱሳን  የአሜሪካና  የአውሮፓ  ንዑሳን ማዕከላት አስተባባሪነት ከጥቅምት ፲-፲፩ ቀን ፳፻፲፩ ዓ.ም/October 20-21/2018  በሰሜን አሜሪካ፣  አትላንታ  ጆርጂያ በ 6202 Memorial Drive Stone Mountain, GA 30083  ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የዓለም አቀፍ ጥናት ጉባኤ ኮሚቴ  ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ (Ludwig Maximilian University, Munich, Germany) እና የኮሚቴ  አባልና የዐውደ ጥናቱ  አስተባባሪ ዶ/ር ፍሬሕይወት ወንድሙ (Wichita State University, USA) በጋራ  እንደገለጹልን  ለሁለተኛ ጊዜ በአሜሪካ አትላንታ ጆርጂያ ከተማ የሚካሄደው  ዓለም አቀፍ የጥናት ጉባኤ፤  የመጀመሪያው  ዓለም አቀፍ ዐውደ ጥናት ጉባኤ በማኅበረ ቅዱሳን አውሮፓ ማእከል  አስተባባሪነት  በስዊድን  ሉንድ  ከተማ በተካሄደበት ወቅት  ከነበረው የዐውደ ጥናቱ  ፋይዳ፣ ቀጣይነትና አቅጣጫዎች በመነሳት  ሁለተኛው  ዐውደ ጥናት በሰሜን አሜሪካ  እንዲሆን መወሰኑን ገልጸዋል፡፡  በተጨማሪም የዐውደ ጥናቱ ዋነኛ ዓላማም  የኢ/ኦ/ተ/ ቤተክርስቲያንን በዓለም አቀፍ መድረክ ማስተዋወቅ ፣ በርካታ ምሥጢራትን ይዘው የሚገኙ  የቤተ ክርስቲያን   ቅርሶቻችን ላይ ጥናትና ምርምር ማድረግ፣ ጥናትና ምርምር  የተደረገባቸውንም  ቅርሶች   በማወያየት ሀብቶቹ የሚጠበቁበትንና  ለተሻለ አገልግሎት የሚበቁበትን  ሁኔታ ማመቻቸት እንደሆነ ገልጸውናል፡፡

የጥናቶቹን  ይዘትና  ማቅረቢያ  ቋንቋ በተመለከተ ለኮሚቴው ተወካዮች ላቀረብነው ጥያቄ፤  ጥናቶቹ  በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የሚቀርቡ ሲሆኑ  በጉባኤው ላይ የሚቀርቡ ጥናታዊ ጽሑፎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚመለከቱ ሆነው፤ የአንድምታ  ትርጓሜ፣ገድላት፣ድርሳናት፣መልክአ መልኮች፣ቅኔ ፣ዜማ ፣የብራና ጽሑፎች  ፣የመድኃኒት ይዘት ያላቸው ጥቅልል ጽሑፎች፣በብራና ውስጥ የሚገኙ ሥዕሎችና በዚህ ዝርዝር ላይ ያልተካተቱ ሌሎች ከጉባኤው ዓላማ ጋር የሚሄዱ ርእሶችም  እንደሚቅቡ  ገልጸውልናል፡፡

 

”ጥናት አቅራቢዎቹ   በቤተክርስቲያናችን ቅርሶች ዙሪያ ጥናታዊ ምርምር የሚያካሂዱ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ዜጎች ሲሆኑ  የጥናት አጠቃሎአቸውን  ኮሚቴው ባስቀመጠው የመገምገሚያ  መስፈርት መሰረት ነጥብ በመስጠት   የተሻለ ነጥብ ያመጡት 13 ጥናቶች ለጉባኤው ሊቀርቡ ዝግጁዎች ናቸው፡፡ የተመረጡት የጽሑፍ አጠቃሎዎች በመጽሔት መልክ ታትመው በጉባኤው የሚሠራጩና በጉባኤው ላይ ቀርበው ውይይት የተደረገባቸውና መመዘኛውን የሚያሟሉ የጥናት ወረቀቶች ደግሞ  በ“የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት መጽሔት” (Journal of Ethiopian Church Studies) እንዲታተሙ ይላካሉ፡፡” ሲሉም አስተባባሪዎቹ ገልጸውልናል፡፡

የጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ  አባላት13 ሲሆኑ  በአውሮፓ፣በአሜሪካና ካናዳ የሚኖሩ የማኀበረ ቅዱሳን አባላትና ደጋፊዎች የሆኑ በተለያዩ  ዩኒቨርሲቲዎች በማስተማርና ጥናትና ምርምር በማድረግ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንናቸው፡፡ በተጨማሪም  የውጭ ሃገር ዜጎች የሆኑ በኢትዮጵያ  ቤተክርስቲያን ታሪክ፣ ዜማና ብራና መጻሕፍት ላይ ምርምር እያደረጉ የሚገኙ  ምሁራን በማማከር ስራዎች እየረዱ እነደሆነም ለመረዳት ችለናል፡፡

 

በዐውደ ጥናቱ ሦስት ቁልፍ ተናጋሪዎች (Keynote Speakers) ሲኖሩ እነዚህም፡-

1.ሊቀ ካህናት ኃይለ ሥላሴ ዓለማየሁ – የዴንቨር ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢ.ኦ.ተ. ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ ሰሜን አሜሪካ፡፡

2.ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ – ሒል ሙዚየም (HMML)፣ ኮሌጅቪል፤ ሰሜን አሜሪካ፡፡

3.ፕሮፌሰር ስቲቭ ዴላማርተር – ጆርጅ  ፎክስ ዩኒቨርሲቲ፣  ሰሜን አሜሪካ  መሆናቸው ተገልጿል፡፡

 

 

መስቀል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን::

  ከጌታችንና ከአምላካችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በፊት መስቀል የመቅጫ መሣሪያ ነበር። ሰውን በመስቀል ላይ መቅጣት የተጀመረውም በፋርስ ነው። ፋርስ የዛሬዋ ኢራን ናት። የፋርስ ሰዎች “ኦርሙዝድ” የተባለ “የመሬት አምላክ” ያመልኩ ነበር። ከዚህም የተነሣ “ወንጀለኛው ቅጣቱን በመሬት ላይ የተቀበለ እንደሆነ አምላካችን ይረክሳል፤” ብለው ስለሚያምኑ ወንጀለኛውን ከመሬት ከፍ አድርገው በመስቀል ላይ ይቀጡት ነበር። ይህም ቅጣት ቀስ በቀስ በሮማ ግዛት ሁሉ የተለመደ ሕግ ሆነ። ከዚህም ሌላ በኦሪቱ ሥርዓት ቅጣታቸውን በመስቀል ላይ የሚቀበሉ ሰዎች ርጉማንና ውጉዛን ነበሩ። ይህንንም እግዚአብሔር ለሙሴ “ማንም ሰው ለሞት የሚያበቃውን ኃጢአት ቢሠራ እንዲሞትም ቢፈረድበት፥ በእንጨትም ላይ ብትሰቅለው፥ በእንጨት ላይ የተሰቀለ በእግዚአብሔር ዘንድ የተረገመ ነውና ሬሳው በእንጨት ላይ አይደር፤” ሲል ነግሮታል። ዘዳ.21፥22-23። እዚህ ላይ “በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የሚሞት የተረገመ ከሆነ፥ ለምን ጌታችን በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ?” እንል ይሆናል። ይህንንም እንደሚከተለው እናያለን።

“ለምን በመስቀል ተሰቅሎ ሞተ?”

ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅሎ ቅዱስ ሥጋውን ቆርሶልናል፥ ክቡር ደሙን አፍስሶልናል፥ ክብርት ነፍሱንም በፈቃዱ አሳልፎ ሰጥቶልናል። ይህንንም ያደረገው በቤዛነቱ እኛን ከእርግማን ሊዋጀን ነው። ምክንያቱም የሰው ልጆች በጠቅላላ በመርገመ ሥጋ በመርገመ ነፍስ ተይዘን ነበርና። በመሆኑም በርደተ መቃብር ላይ ርደተ ገሃነም፥ በሞተ ሥጋ ላይም ሞተ ነፍስ ተፈርዶብን ከእርግማን በታች ወድቀን ነበር። ይሁን እንጂ ፈጣሪያችን “እንደ ወጡ ሳይመለሱ፥ እንደወደቁ ሳይነሱ ይቅሩ፤” ሳይል እኛን ለመፈለግ ከሰማየ ሰማያት ወረደ። ማቴ.18፥12-14። በመንፈስ ቅዱስ ግብር በማኅፀነ ድንግል ማርያም ተፀነሰ። ሉቃ.1፥35። ከእመቤታችንም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነስቶ በቤተልሔም በከብቶች በረት ተወለደ። ሉቃ.2፥7። በተዋህዶ ሰው አምላክ፥ አምላክ ሰው ሆነ። ማቴ.16፥13፣ 1ኛ ዮሐ.1፥1-2፤ 5፥20። ቀስ በቀስም አደገ። ሉቃ.2፥40። ሠላሳ ዓመት በሞላውም ጊዜ በፈለገ ዮርዳኖስ በዕደ ዮሐንስ ከተጠመቀ በኋላ ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄዶ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ጾመ። ማቴ.3፥13-17፣ ሉቃ.3፥21-23፣ ማቴ.4፥2። ከዚያም አሥራ ሁለቱን ደቀ መዛሙርት ሰባ ሁለቱን አርድዕትና ሠላሳ ስድስቱን ቅዱሳት አንስት መረጠ። የሐዋ.1፥15። አዲስ ሕግ ወንጌልንም ሦስት ዓመት ከሦስት ወር አስተማረ። በመጨረሻም ሰለእኛ እርግማን /ኃጢአት/ ተላልፎ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ። ማር.15፥23-37። የሞተውም በፈቃዱ ነው። ዮሐ.10፥11፤ 15፥13። በዚህም የዕለት ፅንስ ሆኖ በእመቤታችን ማኅፀን ጀምሮት የነበረውን የማዳን ሥራ በመስቀል ላይ ፈጸመው። ዮሐ.19፥30።

እንግዲህ ጌታችን ወደዚህ ዓለም መጥቶ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅሎ የሞተው ከላይ እንደተጠቀሰው ስለ እኛ እርግማን ተላልፎ ነው። እርሱ በመስቀል ላይ እርግማናችንን /ኃጢአታችንን/ ሰለተሸከመልንም እኛ ከእርግማን /ከመርገመ ሥጋ፥ ከመርገመ ነፍስ/ ነፃ ሆነናል። ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ “በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፥ ሕመማችንንም ተሸክሟል፤ … እርሱ ግን ስለመተላለፋችን ቆሰለ፥ ስለበደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣፅ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን።” ሲል አስቀድሞ የተናገረው ለዚህ ነው። ኢሳ.53፥4-5። ቅዱስ ጳውሎስም ለገላትያ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ “በእንጨት የሚሰቀል ሁል የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፏልና፥ ክርስቶስ ስለ እርግማን ሆኖ /ስለ እኛ ኃጢአት ተላልፎ በመስቀል/ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤” ብሏል። ገላ.3፥13። በቆሮንቶስ መልእክቱም “የእግዚአብሔር ማደሪያ ለመሆን እኛን ጻድቃን ያሰኘን ዘንድ ስለ እኛ ኃጢአት ተላልፎ ራሱን ኃጥእ አሰኝቷልና፤” ብሏል። 2ኛ ቆሮ.5፥21። ከዚህም ሌላ ለፊሊጵስዩስ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ “ነገር ግን የባርያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ይኸውም ለመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ፤” ብሏል። ፊል.2፥7-8። ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስም በበኩሉ “እርሱ ኃጢአት አላደረገም፥ ተንኰልም በአፉ አልተገኘበትም፤ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም መከራንም ሲቀበል አልዛተም፥ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፥ ኃጢአታችንን /እርግማናችንን/ በእንጨት /በመስቀል/ ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ፤” ብሏል። 1ኛ ጴጥ.2፥22-24። በመሆኑም በመስቀል ላይ በተፈጸመው ቤዛነት ብዙ ነገር አግኝተናል።

1ኛ. ሕይወትን አግኝተናል፤

በኃጢአት ምክንያት ሞት ገዝቶን ሞት ነግሦብን ነበር። ኃጢአት በዘር እየተላለፈም ሁላችንም በአዳም ኃጢአት ምክንያት እንሞት ነበር። በመሆኑም ሞት ከአዳም እስከ ሙሴ /እስከ ክርስቶስ/ ድረስ ነገሠ። ሮሜ.5፥12-14። ከክርስቶስ በኋላ ግን በክርስቶስ ቤዛነት ሞት ስለተሻረ አጥተነው የነበረውን ሕይወት አግኝተናል። ለዚህም ነው “ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና፤” የተባለው። 1ኛ ቆሮ.15፥22። በተጨማሪም “እኛ ሁላችን ደግሞ፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበር እንደሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን። ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለጠጋ ስለሆነ፥ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር /በክርስቶስ ቤዛነት/ ሕይወትን ሰጠን።” ተብሏል። ኤፌ.2፥3-5። ምክንያቱም ጌታችን በሞቱ ሞትን ሽሯልና። 2ኛ. ጢሞ.1፥10።

2ኛ. የሕይወትን ምግብ አግኝተናል፤

ኃጢአት ወደ ዓለም ገብቶ ሞትን ያመጣብን በመብል ምክንያት ነው። ዘፍ.3፥1-24። ምክንያቱም አዳምና ሔዋን የዕፀ በለስን ፍሬ በልተው ጐትተው ያመጡት ሞትን ነውና። ኢዮርብአምን እንዲገሥጽ ተልኮ የነበረውም የይሁዳ ሰው አትብላ የተባለውን በመብላቱ ያተረፈው ሞትን ነው። 1ኛ ነገ.13፥20-25። እስራኤል ዘሥጋም በምድረ በዳ የተመገቡት መና ከሞት አላዳናቸውም። ዮሐ.6፥49። ስለዚህ ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ሥጋውን የሕይወት እንጀራ አድርጎ በመስቀል ላይ ሰጠን። ይህንንም “እውነት እውነት እላችኋለሁ የሰውን ልጅ /የወልደ ዕጓለ እመሕያው ክርስቶስን/ ሥጋውን ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፤” ሲል አረጋግጦልናል። ዮሐ.6፥53-54። በመሆኑም ዕለት ዕለት በቤተክርስቲያን የሚሠዋውና በሃይማኖት የምንቀበለው ቅዱስ ቁርባን አማናዊ የኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና አማናዊ የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ነው። ምክንያቱም ኅብስቱ ተለውጦ ሥጋ መለኰት ወይኑም ተለውጦ ደመ መለኰት ይሆናልና። ማቴ.26፥27-29። ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሳይገባው ይህንን እንጀራ የበላ ወይም የጌታን ጽዋ የጠጣ ሁሉ የጌታ ሥጋና ደም ዕዳ አለበት። ሰው ግን ራሱን ይፈትን፥ እንዲሁም ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤ ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና፤” ያለው። 1ኛ ቆሮ.11፥27-30።

3ኛ. ሰላምን አግኝተናል፤

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፡- “ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም፤” ብሎ እንደተናገረ ፍጹም የሆነውን ሰላም የሰጠን በመስቀል ላይ ነው። ይህንንም፡- ሞትን በኃይሉ ድል አድርጎ በተነሣ ጊዜ “ሰላም ለእናንተ ይሁን፤” በማለት ለደቀ መዛሙርቱ አረጋግጦላቸዋል። ዮሐ.14፥27፤ 20፥19፣26። ይህንን በተመለከተ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “እግዚአብሔር ሙላቱ ሁሉ በእርሱ እንዲኖር፥ በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና፤” በማለት የቆላስይስን ሰዎች አስተምሯል። ቆላ.1፥19-20። የኤፌሶንን ሰዎችም “አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል። እርሱ ሰላማችን ነውና /ሰላማችን የተገኘው በእርሱ ቤዛነት ነውና/፤” ብሏቸዋል። ኤፌ.2፥13።

4ኛ. አዲስ ሰው ሆነናል፤

በመርገመ ሥጋ በመርገመ ነፍስ አርጅቶ የነበረው ሰውነታችን አዲስ የሆነው በመስቀል ላይ በተፈጸመው ቤዛነት ነው። ለዚህም ነው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን /ሰውነታችን/ ከእርሱ ጋር እንደተሰቀለ እናውቃለን።” ያለው ሮሜ.6፥6። ዳግመኛም በቆሮንቶስ መልእክቱ ላይ “ስለዚህ ማንም ቢሆን በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፏል፤ እነሆ ሁሉም አዲስ ሆኗል፤” ብሏል። 2ኛ ቆሮ.5፥17። ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው፡- ጌታችን እኛን በቤዛነቱ አዲስ አድርጎናል፥ አዲስ ሕግ ወንጌልንም ሰጥቶናል፥ አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር መንግሥተ ሰማያትንም አዘጋጅቶልናል። ማር.1፥15፣ 2ኛ ጴጥ.3፥13፣ ራእ.21፥1።

5ኛ. ታርቀናል፤

በኃጢአት ምክንያት ከእግዚአብሔር ጋር ተጣልተን እንኖር ነበር። ይሁን እንጂ እኛ በበደልን እርሱ ክሶ በቤዛነቱ መልሶ ታርቆናል። ይህንንም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ጠላቶቹ ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤ ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን አሁን መታረቁን ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ደግሞ እንመካለን፤” ሲል ገልጦታል። ሮሜ.5፥10-11። በተጨማሪም “በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዷልና፤” ብሏል። ቆላ.1፥20። በኤፌሶን መልእክቱም “ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛት ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳ በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድ አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር /ከራሱ/ ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው፤” ብሏል። ኤፌ.2፥14-16፣ 2ኛ ቆሮ. 5፥17። በመሆኑም ይህ ሁሉ ነገር የተገኘበት መስቀል፡-

ኃይላችን ነው፤

“የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና፤” 1ኛ ቆሮ.1፥18 ተብሎ እንደተነገረ፥ የእግዚአብሔር ኃይሉ የተገለጠበት ኃይለ እግዚአብሔር ክርስቶስ የማዳን ሥራውን የፈጸመው በመልዕልተ መስቀል ተሰቅሎ ነው። በመሆኑም የጌታችን ቅዱስ ሥጋው የተፈተተበትና ክቡር ደሙም የፈሰሰበት መስቀል ስለ ክርስቶስ የከበረ ነው። ለምሳሌ የሆሳዕና አህያ በተጓዘችበት ጐዳና ሁሉ የተነጠፈላትና የተጐዘጐዘላት ስለ ክርስቶስ የከበረች በመሆኗ ነው። ማቴ.21፥8። ስለዚህ ስለ ክርስቶስ የከበረውና የማዳን ኃይሉም የተገለጠበት መስቀል፥ ወልድ ዋህድ ብለን በኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክነት ለምናምን ሁሉ ዲያብሎስን የምንቀጠቅጥበት ኃይላችን ነው። ምክንያቱም ጌታችን አስቀድሞ “እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል፤” ተብሎ እንደተነገረ ዲያብሎስን የቀጠቀጠው በመስቀሉ ነውና። ዘፍ.3፥15። ይህንን በተመለከተ በብሉይ ኪዳን ዘመን የተፈጸመ ምሳሌ አለ። የነቢያት አለቃ ሙሴ እጆቹን በመስቀል አምሳል ግራና ቀኝ ዘርግቶ በሚጸልይበት ጊዜ እስራኤል ኃይል አግኝተው ጠላቶቻቸውን ድል አድርገዋል። እኛም እስራኤል ዘነፍስ የምንባል ምዕመናንም ጠላቶቻችንን አጋንንትን በኃይለ መስቀሉ ድል እናደርጋቸዋለን። የአሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል አባት ቅዱስ ያዕቆብም እጆቹን ባመሳቀለ ጊዜ ኃይል አግኝቶ በዮሴፍ ልጆች ላይ በረከትን አሳድሯል። ዘፍ.48፥13-20። እኛም በመስቀሉ ኃይል በረከተ ሥጋንና በረከተ ነፍስን እናገኛለን።

ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ ግን ፊት በቀራንዮ ድል የሆነበትን፥ ኋላም እንደ ቀራንዮ ዕለት ዕለት የክርስቶስ ሥጋውና ደሙ በሚፈተትባት በቤተክርስቲያን ድል የሚሆንበትን መስቀል ከእጃችን ለማስጣል ያልሞከረው ሙከራ የለም። ለልማዱም “እንጨት አይደል? ለምን ትሳለሙታላችሁ? ለምንስ ትሰግዱለታላችሁ?” እያሰኘ ነው። ይሁን እንጂ በቤተክርስቲያን በክርስቶስ ኃይል ይታመናል እንጂ “ይህ እንጨት ነው፥ ይህም ጨርቅ ነው፥ ይህ ደግሞ ውሃ ነው፤” ተብሎ አይጠረጠርም። ለምሳሌ፡-
•    በትረ ሙሴ ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦባት ብዙ ተዓምራት አድርጋለች፤ ከዘፀ.4-14
•    የኤልያስ መጐናጸፍያ ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦባት ዮርዳኖስን ከአንዴም ሁለት ጊዜ ለሁለት ከፍላለች፤ 2ኛ ነገ.2፥7-14
•    ፈለገ ዮርዳኖስ ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦባት ንዕማንን ከለምጹ ፈውሳዋለች፤ 2ኛ ነገ.5፥1-14
•    በዘይት /በቀንዲል/ ላይ ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦ በሽተኞች ተፈውሰዋል፤ ማር.6፥13፣ ያዕ.5፥14
•    የቤተሳይዳ መጠመቂያ ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦባት ዓይነ ስውሩ ብርሃን አግኝቶባታል፤ ዮሐ.9፥1-12
•    ቅዱስ ጳውሎስ የልብሱ ቁራጭ ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦበት ብዙ በሽተኞች ፈውስ አግኝተውባታል፤ ከአጋንንት ቁራኝነትም ተላቀውባታል፤ የሐዋ.19፥11-12
•    ቅዱስ ጴጥሮስ ጥላው ኃይለ እግዚአብሔር ተገልጦባት ከመንገድ ዳር የወደቁ በሽተኞች ሁሉ ተፈውሰውባታል። የሐዋ.5፥15። ስለሆነም ስለመስቀሉ ያልሆነ ነገር እየተናገርን ከመስቀሉ ባለቤት ከክርስቶስ እንዳንጣላ መጠንቀቅ አለብን። ምክንያቱም መስቀልን መጥላት የክፉ ትንቢት መፈጸሚያ መሆን ነውና። ይህንንም በተመለከተ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ፥ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ አላለሁ። መጨረሻቸው ጥፋት ነው /ገሃነመ እሳት ነው/፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው /አይጾሙም/፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው፤” ሲል ተናግሯል። ፊል.3፥18-19።

እንግዲህ ነቢዩ ዳዊት “ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው። ወዳጆችህ እንዲድኑ፤” ብሎ አስቀድሞ በትንቢት እንደተናገረ፥ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዲያብሎስ ቀስት /ጦር/ እናመልጥና እንድን ዘንድ በደሙ ቀድሶና አክብሮ የሰጠንን ምልክት መስቀልን አጥብቀን መያዝ አለብን። መዝ.59፥4-5። እንደ ቅዱስ ጳውሎስም “ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት /ዓለም በእኔ ዘንድ ሙት ከሆነበት/ እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት /እኔም በዓለም ዘንድ ሙት ከሆንኩበት/ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።” እያልን በመስቀሉ መመካት አለብን። ገላ.6፥14። መስቀልን በምልክትነቱ ብቻ የሚቀበሉት ሰዎች አሉ፤ ለእኛ ግን መስቀል ኃይላችን፥ መድኃኒታችን፥ የሚያድነን፥ ቤዛችንና የነፍሳችንም መዳኛ ነው። ከዚህ ቀጥለን ደግሞ የምናየው በዓለ መስቀልን ለምን እንደምናከብር ነው።

የመስቀልን በዓል ለምን እናከብራለን?

የመስቀል በዓል የሚከበረው መስከረም 17 ቀን ነው። የሚከበርበትም ምክንያት፡- ጌታ በመስቀል ላይ ሙቶ ከተነሣ በኋላ ሕሙማን መስቀሉን እየዳሰሱ በመስቀሉ እየታሹ ይፈውሱ ነበር። ይህንን ያዩ አይሁድም በምቀኝነት መስቀሉን ከቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቦታ ጣሉት። ከብዙ ጊዜም በኋላ ያ ቦታ እንደ ጉብታ ሆነ። ምንም እንኳ ለማውጣት ባይችሉ ክርስቲያኖቹ ያን ቦታ ያውቁት ነበር። በኋላ ግን በ70 ዓ.ም. በጥጦስ ወረራ ክርስቲያኖቹ ኢየሩሳሌምን ለቀው ስለወጡና የከተማዋም መልክ ስለተለወጠ መስቀሉ የተቀበረበትን ጉብታ ለማወቅ አልተቻለም። በዚህም ምክንያት ለሦስት መቶ ዓመታት ያህል ተዳፍኖ ቆይቷል። በኋላ ላይ ግን በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የታላቁ ንጉሥ የቆስጠንጢኖስ እናት ንግሥት እሌኒ ወደ ኢየሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን ለማውጣት ብዙ ደከመች። በመጨረሻም ስሙ ኪርያኮስ የተባለ አረጋዊ በነገራት መሠረት ደመራ አስደምራ ዕጣን አፍስሳበት በእሳት ብትለኩሰው ጢሱ እንደ ቀስተ ደመና መስቀሉ ከተቀበረበት ጉብታ ላይ ተተክሎ በጣት ጠቅሶ የማሳየት ያህል አመልክቷታል። ሳትውል ሳታድር መስከረም 17 ቁፋሮ አስጀምራ መጋቢት 10 መስቀሉን አግኝታለች። ቅዳሴ ቤት /ቤተመቅደስ/ ተሠርቶ የተፈጸመው በመስከረም 17 ነው።  እንደወጣም ብዙ ተዓምራትን አድርጓል።

እንግዲህ በሀገራችን በኢትዮጵያ የመስቀልን በዓል ደመራ በመደመርና ችቦ በማብራት፥ ቅዳሴ በመቀደስና ማኅሌት በመቆም የምናከብረው ለዚህ ነው። በዚሁም ላይ ይህን ታላቅ ዕፀ መስቀል በወቅቱ የነበሩ ታላላቅ ነገሥታት የሚያደርጋቸውን ተዓምራት በማየት ለእያንዳንዳቸው ይደርሳቸው ዘንድ ከአራት ክፍል ሲከፍሉት ከአራቱ አንዱ የቀኝ እጁ ያረፈበት ግማድ /ክፋይ/ ብቻ በደብረ ከርቤ ግሸን ማርያም ሲገኝ ሌሎች ሦስቱ ግን የት እንደደረሱ አይታወቅም። ይህም ግማደ መስቀል የመጣው በአፄ ዳዊት በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሲሆን ኢትዮጵያ ከገባ በኋላ የማስቀመጫ መቅደስ ለማሠራት መሬቱ እየተንቀጠቀጠ አልረጋ ብሏቸው በርካታ አድባራትን ካዳረሱ በኋላም እግዚአብሔር “አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል /መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አስቀምጥ/” ብሎ ስለነገራቸው ተፈልጋ ግሸን ደብረ ከርቤ በተባለው ቦታ የመስቀል ቅርጽ ስለተገኘች ዛሬም ድረስ በዚሁ ታላቅ ቦታ ይገኛል። በዚህ ታላቅ ጸጋ የተጠቀሙት ብዙዎች ናቸውና እኛንም ከዚህ ረድኤት እንዲከፍለን በዓሉን በአግባቡና በሥርዓት ልናከብረው ያስፈልጋል። መልካም በዓል አክብረን የመስቀሉ ክብርና ጸጋ ረድኤት ይድረሰን። አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

አዘጋጅ፡-
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን
የአሜሪካ ማዕከል የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል   
2006 ዓ.ም.